ዜና | Oduu | News
"የሸማች ማህበራት ሪፎርም እና ገበያ ማረጋጋት ስራችን የለውጡ አንድ አካል ናቸው።" ክቡር አቶ ጃንጥራር አባይ

በልደታ ክፍለ ከተማ አዲስ ሚሊኒየም ሸማቾች ህብረት ስራ ማህበር የገበያ ማዕከል በዛሬው እለት በድምቀት ተመርቆ ለግብይት ክፍት ሆነ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር አቶ ጃንጥራር አባይ በገበያ ማዕከሉ ምረቃ ፕሮግራም ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉ ሲሆን የሸማች ማህበራት ሪፎርም እና ገበያ ማረጋጋት ስራችን የለውጡ አንድ አካል ናቸው ብለዋል። ሸማች ማህበራቱ የምርት አቅርቦች ችግር በሚኖርበት ጊዜ መልስ ሰጪ ናቸው ያሉት ክቡር ምክትል ከንቲባው በበዓላት ወቅት የሚከሰተውን ሰው ሰራሽ የምርት እጥረት እና የዋጋ ንረት ለመከላከል ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ገልፀዋል። ክቡር አቶ ጃንጥራር አያይዘው በአሁኑ ወቅት በመካከለኛው ምስራቅ የተከሰተው አጠቃላይ አለማቀፋዊ ቀውስን ታሳቢ ያደረገ የዋጋ ማረጋጋትና የምርት አቅርቦት ላይ የከተማ አስተዳደሩ ከአምራች አርሶ አደሮች በቀጥታ ለሸማቹ እንዲደርስ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል ብለዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ በበኩላቸው እንደነዚህ አይነት የገበያ ማዕከላት ተደራሽ ማድረግ ህብረተሰቡ በህገወጥ ደላሎች እና በትራንስፖርት ችግር ይደርስበት የነበረውን እንግልት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንሰው አስገንዝበዋል። ወ/ሮ ሊዲያ አያይዘው የበዓላት ወቅት በመጠቀም ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ፣ በምርቶች ላይ ባዕድ ነገሮችን የሚቀላቅሉ፣ በመጋዘን በህገወጥ መንገድ የሚከዝኑ እንዲሁም ከሀሰተኛ የብር ኖት ግብይት ጋር በተያያዘ ማህበረሰቡ ራሱን እንዲጠብቅና ለሚመለከተው የህግ አካል ጥቆማ እንዲያደርግ አሳስበዋል። የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንዳሉት የፋሲካ በዓል ባዛር ምክንያት በማድረግ በዛሬው እለት የተከፈተው ማዕከል ከዚህ ቀደም ለግለሰቦች በኪራይ መልክ በማስተላለፍ ለጥቂቶች መጠቀሚያ የነበረ ሲሆን ሆኖም አስተዳደሩ በጀመረው ሪፎርም መሠረት አሁን ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶችን የሚያቀርብ የገበያ ማዕከል ማድረግ መቻሉን ጠቁመዋል። የኑሮው ውድነት የማረጋጋት ስራ ከሌሎች ፕሮጀክቶች ባልተናነሰ የቅድሚያ ቅድሚያ እየተሰጠው መሆኑን የተናገሩት ወ/ሮ ልዕልቲ የከተማው አስተዳደር የኑሮ ውድነትና ገበያ ማረጋጋት ግብረ ሀይል ትላልቅ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በተያያዘ 'በቂ አቅርቦት ከአምራች እስከ ሸማች በተመጣጣኝ ዋጋ ለፋሲካችን' በሚል መሪ ቃል የመጪው የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በክፍለ ከተማው የተለያዩ ወረዳዎች በሚገኙ የበዓል ባዛር እና ኤግዝቢሽን ማዕከላት በተመጣጣኝ ዋጋ የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶች እየቀረበ ይገኛል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክፍለ ከተማ ንግድ ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወር አፈፃፀም እውቅናና ሽልማት አካሄደ።

በመድረኩም የ2018 በጀት አመት የቀሪ 6 ወራት የተከለሰ እቅድ የጋራ ተደርጓል። በእውቅናና ሽልማቱ የወረዳ አመራሮች ፣ የምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች እንዲሁም የዘርፉ ሰራተኞችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወር አፈፃፀም እውቅናና ሽልማት ተሰጥቷል። የልደታ ክፍለ ከተማ ንግድ ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ተስፋነሽ ጋሻው በእውቅናና ፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት ባሳለፍነው 6 ወር የተሻለ የንግድ ስርዓት እንዲኖር ወጥ የሆነ እቅድ ታቅዶ ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀው እቅዱ ተግባራዊ እንዲሆን ውጤታማ የሆነ ድጋፍና ክትትል መደረጉን ተናግረዋል:: የንግድ ስርዓቱን በማዘመንና በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ በማድረግ ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት መስጠት ያስፈልጋል ያሉት ወ/ሮ ተስፋነሽ ጋሻው አያይዘው ገበያውን ለማረጋጋት የተቋቋሙት የእሁድ ገበያ መዳረሻ ቦታዎች በቂ የምርት አቅርቦት እንዲኖርና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲሸጥ አስፈላጊውን ድጋፍና ተገቢውን ቁጥጥር በማድረግ ባሳለፍነው 6 ወር የተሻለና ውጤታማ ስራዎች መሰራቱን ተናግረዋል:: የልደታ ክፍለ ከተማ ንግድ ፅ/ቤት በ2018 በጀት አመት የ6 ወር የዕቅድ አፈፃፀም ምዘና በማድረግ የላቀ አፈፃፀም ለነበራቸው ተቋማትና ባለሙያዎች ዕውቅናና ማበረታቻ ሽልማት በሰጠበት በበጀት አመቱ በ6 ወሩ ውስጥ ደረጃ ውስጥ ለገቡ ወረዳዎች የዋንጫ እና የሰርተፍኬት ሽልማት ተሰጥቷቸዋል። በዚህም መሰረት :- ወረዳ 8 ንግድ ጽ/ቤት 1ኛ ወረዳ 4 ንግድ ጽ/ቤት 2ኛ ወረዳ 1 እና 10 ንግድ ጽ/ቤት 3ኛ በመሆን የዋንጫ ተሸላሚ ሆነዋል። በቅዳሜና እና እሁድ ገበያ ስታንዳርድ በማስጠበቅ ወረዳ 7 የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
ለበርካታ ዓመታት በጉልት ንግድ ተሰማርተው የነበሩ 69 እናቶችን ወደ ዘመናዊ የንግድ ማዕከል ማስገባት ተችሏል።

ዜጎችን ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለመቀየር በተሰራ ስራ ለበርካታ ዓመታት በጉሊት ንግድ ላይ ተሰማርተው በፀሀይና በብርድ ሲሰቃዩ የነበሩ 69 እናቶችን ወደ ዘመናዊ የንግድ መዋቅር ማሸጋገር ተችሏል።

image
image
image
image