image
image
image
image
image

የንግድ ተቋማት የምሽት ስራ ጉብኝትና የቁጥጥር ስራ ተካሄደ።

ሰኔ 24, 2018
በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 3 አስተዳደር ስር የሚገኙ የንግድ ተቋማት እስከ ምሽቱ 3:30 ድረስ እንዲሰሩ የወጣው ደንብ ቁጥር 185/2017 አስመልክቶ የገበያ ማረጋጋት ግብረ ሀይል ለንግድ ተቋማቱ ግንዛቤ እና የቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል በቁጥጥር ተግባሩ ላይ የልደታ ክፍለ ከተማ ንግድ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ተስፋነሽ ጋሻው እና የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ደሳለኝ ካሴ በተገኙበት ተካሂዷል። በምሽት የንግድ አገልግሎት እንዲሰጥ የወጣውን ደንብ ቁጥር 185/2017 አስመልክቶ የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 የገበያ ማረጋጋት ግብረ ሀይል አባላት በጋራ በመሆን በወረዳ ውስጥ ተዘዋውረው ምልከታና ቅኝት አድርገዋል:: በምሽት የንግድ አገልግሎት እንዲሰጥ የተፈለገው የከተማዋን ፈጣን እድገት ተከትሎ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማሳደግ እንደሆነ በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች