image
image
image
image
image

የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር አሁን ያለውን አለም አቀፋዊ የኑሮ ውድነት ለማርገብ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።

ሰኔ 28, 2018
ነዋሪዎችን ካልተገባ ወጭና እንግልት የታደገው ገበያ ። ከነዚህ ተግባራት ውስጥ አንዱ ደግሞ የእሁድ ገበያን ተደራሽነት ማስፋትና ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲቀርቡ ማስቻል ነው። አስተዳደሩ 11 የእሁድ ገበያ መዳረሻ ስፍራዎች በማዘጋጀት ማህበረሰቡ ምርቶችን በሚቀርበው ቦታ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲገዛ አስችሏል። የምርት እጥረት እንዳይከሰትም የገበያ ትስስርን በመፍጠር ምርቶች ከገበሬውና ከአምራች ኢንዱስትሪዎች በቀጥታ ለሸማቹ እንዲቀርቡ አድርጓል እያደረገም ነው። ማህበረሰቡም የእሁድ ገበያ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ ከህገ-ወጥ ነጋዴዎችና ደላሎች ብዝበዛ ተላቋል። ሸማቹ ምርት ለመግዛትም ሆነ የገዛውን ምርት ለማስጫን ለትራንስፖርት ያወጣው የነበረን ወጭም መቀነስ ተችሏል ። እርስዎስ ዛሬ እረፍትዎም አይደል በአቅራቢያዎ ባለው የእሁድ ገበያ ጎራ ብለው ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ይግዙና የእሁድ ገበያን ቱርፋት ያጣጥሙ እንላለን። የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች